عربيEnglish

The Noble Qur'an Encyclopedia

Towards providing reliable exegeses and translations of the meanings of the Noble Qur'an in the world languages

The Mansions of the stars [Al-Burooj] - Amharic translation - Africa Academy

Surah The Mansions of the stars [Al-Burooj] Ayah 22 Location Maccah Number 85

1. የህብረ ከዋክብት ባለቤት በሆነችው ሰማይ፤

3. በመስካሪና በሚመሰከርበትም እምላለሁ::

4. የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ::

5. የባለማገዶዋ እሳት ባለቤቶች።

6. እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በሆኑ ጊዜ (ተረገሙ)።

7. እነርሱም በምዕመኖች ላይ ለሚሰሩት (ማሰቃየት) መስካሪዎች ናቸው።

8. ከእነርሱም በአሸናፊውና በምስጉኑ ጌታ ማመናቸውን እንጂ ሌላን ምንንም አልጠሉም::

9. ያ የሰማይና የምድር ንግስና ለእርሱ ብቻ የሆነውን (ነው ያመኑበት)። አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው (አዋቂ ነው)።

10. እነዚያ አማኞችና ምዕመናትን ያሰቃዩና ከዚያ ያልተጸጸቱ ሁሉ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አለላቸው:: ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው::

11. እነዚያ በአላህ አምነው መልካም ስራዎችን የሰሩ ሁሉ ለእነርሱ ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው:: ይህ ታላቅ ስኬት ነው::

12. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህ በኃይል መያዝ ብርቱ ነው።

13. እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም::

14. እርሱም ምህረቱ የበዛ ወዳድ ነው::

15. የላቀው የዙፋኑ ባለቤት ነው።

16. የሚሻውን ሁሉ ሰሪ (ፈፃሚ) ነው::

17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! የእነዚያ ነብያትን ያስተባበሉ) ሰራዊቶች ወሬ መጣልህን?

18. የፊርዓውንና የሰሙድ (ወሬ ደርሶሃልን)?

19. በእውነት እነዚያ (በአላህ) የካዱት (ሰዎች ሁሉ) እውነትን በማስተባበል ውስጥ ናቸው::

20. አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው::

21. ይልቁንም እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::

22. የተጠበቀ በሆነ ሰሌዳ (ሎህ) ውስጥ ነው::