عربيEnglish

The Noble Qur'an Encyclopedia

Towards providing reliable exegeses and translations of the meanings of the Noble Qur'an in the world languages

The Overwhelming [Al-Ghashiya] - Amharic translation - Africa Academy

Surah The Overwhelming [Al-Ghashiya] Ayah 26 Location Maccah Number 88

1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሸፋኝቱ ትንሳኤ ወሬ መጣልህን?

2. በዚያ ቀን የከሓዲያን ፊቶች ተዋራጆች ናቸው::

3. ሰሪዎች ለፊዎች ናቸው::

4. የምታቃጥልን እሳት ይገባሉ::

5. በጣም ከፈላች ምንጭም ይጋታሉ::

6. ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃማ) ዛፍ እንጂ ሌላ ምግብ የላቸዉም::

7. አካልን አያሰባ፤ ከረኃብም አያብቃቃ፤

8. (የአማንያን) ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው::

9. በስራቸውም ተደሳቾች ናቸው::

10. በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው::

11. በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም::

12. በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አሉ::

13. በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አሉ::

14. በተርታ የተኖሩ ኩባያዎችም፤

15. የተደረደሩ መከዳዎችም፤

16. የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አሉ)::

17. (ከሓዲያን) ግመል እንዴት እንደተፈጠረች አይመለከቱምን?

18. ሰማይም እንዴት ከፍ እንደተደረገች!

19. ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!

20. ምድርም እንዴት እንደተዘረጋች አይመለከቱምን?!

21. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አስታውስም:: አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና::

22. በእነርሱ ላይ አስገዳጅ (ተሿሚ) አይደለህም፤

23. ግን ከእውነት የዞረና የካደ፤

25. መመለሻቸው ወደ እኛ ብቻ ነው::

26. ምርመራቸዉም በእኛ ላይ ብቻ ነው::