عربيEnglish

The Noble Qur'an Encyclopedia

Towards providing reliable exegeses and translations of the meanings of the Noble Qur'an in the world languages

The Fig [At-Tin] - Amharic translation - Africa Academy

Surah The Fig [At-Tin] Ayah 8 Location Maccah Number 95

1. በበለስና፤ በወይራ ዛፍ እምላለሁ፣

2. በሲና ተራራም፤

3. በዚህ በጸጥተኛው (ጸጥታ በነገሰበት) አገር መካም እምላለሁ።

4. በርግጥ ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው::

5. ከዚያም (ከፊሉን) ከበታቾች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው::

6. እነዚያ በአላህ ያመኑትና መልካም ተግባራት የሰሩት ሲቀሩ ለእነርሱማ የማይቋረጥ ምንዳ አለላቸው::

7. (የሰው ልጅ ሆይ) ታዲያ ከዚህ (እውነታ) በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?

8. አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን?